First-born ~ በኩር: (ዘዳ 21፡17) ... [Related
term(s):- Becher, Baruch]
Sons
enjoyed certain special privileges, “But he shall acknowledge the son
of the hated for the firstborn, by
giving him a double portion of all that he hath: ...” (Deut 21:17)
-------------------------------------------------------------------------------------------------
-------------------------------------------------------------------------------------------------
በኩር ~First-born: ብኵር፣ የመጀመሪያ ልጅ፣ በኵሬ ማለት ነው።
[ተዛማጅ ስሞች- በኵር፣ በኵሬ፣ ቢክሪ ፣ ቢክሪ፣ ቤኬር፣ ብኵር፣ ብኮራት፣ ቦክሩ]
‘በከረ’ ከሚለው ግስ የተገኘ ስም ነው።
[ከሰው ወይም ከከብት መጀመሪያ የሚወለድ / መቅቃ]
v
የኃይሉ መጀመሪያ፥ “ነገር ግን ከከብቱ ሁለት እጥፍ ለእርሱ በመስጠት ከተጠላችው ሚስት የተወለደው ልጅ በኵር እንደ
ሆነ
ያስታውቅ።
የኃይሉ መጀመሪያ ነውና በኵርነቱ የእርሱ ነው።” (ዘዳ 21፡17)
v
በኢሳው ፋንታ ያዕቆብ በኩር ተብሎ ተጠራ፥ “...ታላቁም
ለታናሹ ይገዛል።” (ዘፍ 25:23) ያዕቆብም፦
በመጀመሪያ ብኵርናህን ሽጥልኝ አለው። ...
ዔሳው ብኵርናውን አቃለላት።” (34)፣ “...
በኵርነቱን እንደ
ሸጠ እንደ ዔሳው ለዚህ ...” (ዕብ12:16)
v
የያቆብ ልጅ
ሮቤል፥
“ሮቤል፥
አንተ በኵር
ልጄና ኃይሌ...” (ዘፍ 49:3) “የእስራኤልም በኵር የሮቤል
ልጆች ...” (1 ዜና 5:1)
v
እስራኤል
የእግዚአብሔር የበኩር ልጅ ተብሎ ተጠራ፥ “እስራኤል የበኵር
ልጄ ነው ይገዛልኝ ዘንድ ልጄን ልቀቅ አልሁህ አንተም ትለቅቀው ዘንድ እንቢ አልህ እነሆ እኔ የበኵር ልጅህን እገድላለሁ ትለዋለህ።” (ዘጸ 4:23)
v ንጉሥ ዳዊት ስለ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በተናገረው ትንቢት በኩር ብሎ ጠርቶታል፥“እኔም ደግሞ በኵሬ አደርገዋለሁ፥ ከምድር ነገሥታትም ከፍ ይላል።” (መዝ 89:27)
No comments:
Post a Comment